አማራ ባንክ እና የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የመጋዘን ደረሰኝ ብድር አገልግሎት ዙሪያ የስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ
አማራ ባንክ ሰፊው ህብረተሰብ ተጠቃሚ የሚሆንበትን የመጋዘን ብድር አገልግሎት ለማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ጋር በዛሬው ዕለት የተፈራረመ ሲሆን በስምምነት ስነስርዓቱ ላይ የአማራ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሔኖክ ከበደ እና የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወንድማገኘሁ ነገራ እንዲሁም የባንኩ እና የምርት ገበያው ከፍተኛ ስራ አስፈፃሚ አባላት ተገኝተዋል፡፡
አማራ ባንክ በአብዛኛው ኢመደበኛ በሆነው የፋይናንስ አገልግሎት ብቻ ተወስኖ የሚንቀሳቀሰውን ሰፊውን የህብረተሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ በሰፊው እየሰራ ሲሆን በመጋዘን ደረሰኝ ብድር አገልግሎትም ባንኩ አካታች የሆነ መደበኛ የፋይናንስ አገልግሎት ለሰፊው ተጠቃሚ ህብረተሰብ ክፍል ለማድረስ የሚያስችለውን ዕድል እንደሚፈጥርለት ተነግሯል፡፡
አማራ ባንክ
ከባንክ ባሻገር!